Thursday 15 May 2014

መድረክ:- ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ለአዲስ አበባ እና ለአከባቢዋ ነዋሪዎች በሙሉ Posted: Caamsaa/May 15, 2014 · Gadaa.com መድረክ በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ መንግስት ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን በኃይል ለማፈን የሚወስዳቸው የኃይል እርምጃዎች እና ተፅዕኖዎች በአስቸኳይ ቆመው የሀገራችን ወቅታዊ እና መሰረታዊ ችግሮች በሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ አግባብ እንዲፈቱ መንግስትን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚካሄድ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ስለዚህም የአዲስ አበባ እና የአከባቢዋ ነዋሪዎች ልክ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ከአራት ኪሎ በስተምስራቅ ወ.ወ.ክ.ማን አለፍ ብሎ ከሚገኘው የግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ተነስቶ በሺ ሰማኒያ፣ በሚስማር ፋብሪካ እና በቀበና ወንዝ ድልድይ አድርጎ እንግሊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ከሚያልፈው መንገድ ላይ ወደ ባልደራስ ታጥፎ በኤካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ኳስ ሜዳ /ታቦት ማደሪያ/ በሚባለው የመሰብሰቢያ ቦታ ድረስ በመገኘት የሰላማዊ ሰልፉ ተካፋይ እንዲሆኑ መድረክ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡ - መድረክ ——————— መድረክ - ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ የመቃወም መብታችንን በኃይል ማፈን ይቁም! - ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ማሰር፣ መግደል እና ማሰቃየት ይቁም! - በመሰብሰብ፣ በመደራጀት፣ ሰላማዊ ሰልፎችን በማድረግ፣ ሀሳብን በነፃነት በመግለጽ እና መረጃ ማግኘት ህገመንግስታዊ መብታችን ላይ የሚፈፀሙት ተፅዕኖዎች ይቁሙ! በሚሉ እና በመሳሰሉት አላማዎች እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከ3 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚካሄድ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ እርስዎም በተጠቀሰው እለት እና ሰዓት መነሻው ከግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ሆኖ መድረሻው በኤካ ክ/ከተማ በወረዳ 8 ኳስ ሜዳ ድረስ በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ጠርተንዎታል፡፡

መድረክ:- ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ለአዲስ አበባ እና ለአከባቢዋ ነዋሪዎች በሙሉ

መድረክ:- ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ለአዲስ አበባ እና ለአከባቢዋ ነዋሪዎች በሙሉ

መድረክ በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ መንግስት ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን በኃይል ለማፈን የሚወስዳቸው የኃይል እርምጃዎች እና ተፅዕኖዎች በአስቸኳይ ቆመው የሀገራችን ወቅታዊ እና መሰረታዊ ችግሮች በሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ አግባብ እንዲፈቱ መንግስትን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚካሄድ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡
ስለዚህም የአዲስ አበባ እና የአከባቢዋ ነዋሪዎች ልክ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ከአራት ኪሎ በስተምስራቅ ወ.ወ.ክ.ማን አለፍ ብሎ ከሚገኘው የግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ተነስቶ በሺ ሰማኒያ፣ በሚስማር ፋብሪካ እና በቀበና ወንዝ ድልድይ አድርጎ እንግሊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ከሚያልፈው መንገድ ላይ ወደ ባልደራስ ታጥፎ በኤካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ኳስ ሜዳ /ታቦት ማደሪያ/ በሚባለው የመሰብሰቢያ ቦታ ድረስ በመገኘት የሰላማዊ ሰልፉ ተካፋይ እንዲሆኑ መድረክ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
- መድረክ
———————
መድረክ
- ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ የመቃወም መብታችንን በኃይል ማፈን ይቁም!
- ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ማሰር፣ መግደል እና ማሰቃየት ይቁም!
- በመሰብሰብ፣ በመደራጀት፣ ሰላማዊ ሰልፎችን በማድረግ፣ ሀሳብን በነፃነት በመግለጽ እና መረጃ ማግኘት ህገመንግስታዊ መብታችን ላይ የሚፈፀሙት ተፅዕኖዎች ይቁሙ!
በሚሉ እና በመሳሰሉት አላማዎች እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከ3 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚካሄድ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡
እርስዎም በተጠቀሰው እለት እና ሰዓት መነሻው ከግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ሆኖ መድረሻው በኤካ ክ/ከተማ በወረዳ 8 ኳስ ሜዳ ድረስ በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ጠርተንዎታል፡፡
ስለዚህም የአዲስ አበባ እና የአከባቢዋ ነዋሪዎች ልክ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ከአራት ኪሎ በስተምስራቅ ወ.ወ.ክ.ማን አለፍ ብሎ ከሚገኘው የግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ተነስቶ በሺ ሰማኒያ፣ በሚስማር ፋብሪካ እና በቀበና ወንዝ ድልድይ አድርጎ እንግሊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ከሚያልፈው መንገድ ላይ ወደ ባልደራስ ታጥፎ በኤካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ኳስ ሜዳ /ታቦት ማደሪያ/ በሚባለው የመሰብሰቢያ ቦታ ድረስ በመገኘት የሰላማዊ ሰልፉ ተካፋይ እንዲሆኑ መድረክ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
- መድረክ
———————
መድረክ
- ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ የመቃወም መብታችንን በኃይል ማፈን ይቁም!
- ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ማሰር፣ መግደል እና ማሰቃየት ይቁም!
- በመሰብሰብ፣ በመደራጀት፣ ሰላማዊ ሰልፎችን በማድረግ፣ ሀሳብን በነፃነት በመግለጽ እና መረጃ ማግኘት ህገመንግስታዊ መብታችን ላይ የሚፈፀሙት ተፅዕኖዎች ይቁሙ!
በሚሉ እና በመሳሰሉት አላማዎች እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከ3 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚካሄድ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡
እርስዎም በተጠቀሰው እለት እና ሰዓት መነሻው ከግንፍሌ ወንዝ ድልድይ ሆኖ መድረሻው በኤካ ክ/ከተማ በወረዳ 8 ኳስ ሜዳ ድረስ በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ጠርተንዎታል፡፡

No comments:

Post a Comment